ሚያዝያ 1 ቀን 2014 ዓ.ም
የተወደዳችሁ የአብርሆተ ሰብእ የትምህርት፣ሥልጠናና ንግድ አ.ማ. ቤተሰቦች አክሲዩኑ ከተመሠረተና ሕጋዊ ዕውቅና ካገኘበት ጊዜ ጀምሮ የዕጣ ሽያጭ እያደረገ እንዲሁም በተጓዳኝ በተመረጡ ዘርፎች ወደ ሥራ የገባ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ሆኖም የአብርሆት ቤተሰብ ለመሆን የዕጣ ሽያጭ ጊዜው እንዲራዘም በተደጋጋሚ ከአዳዲስ አባላትን ጥያቄ
የቀረበ በመሆኑ የአክሲዩኑ የዳይሬክተሮች ቦርድና ሥራ አመራር አዳዲስ አባላትን ቤተሰብ ማድረግ ለሁላችንም የሚኖረውን ፋይዳ ያመነበት በመሆኑ የአክሲዩን ዕጣ ሽያጭ የካፒታል ከ25,000 ብር ጀምሮ ከ10% ስራ ማስኬጃ ጋር በመክፈል እስከ ሰኔ 30/2014 ዓ.ም መስራች አባል መሆን የተፈቀደ መሆኑን ሲያበስር በደስታ ነው!!
ኑ! ትውልድ እንሥራ!!
የዳይሬክተሮች ቦርድና ሥራ አመራር