አብርሆተ ሰብእ የትምህርት ሥልጠናና ንግድ አ/ማ

የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ ጥሪ

ጤና ይስጥልን የተከበራችሁ የአብርሆተ ሰብእ የት/ት ሥልጠናና ንግድ አ.ማ ባለ አክሲዮኖች!!

አክሲዩኑ በቀጣይ ሥራዎቹ ላይ ውሳኔ ለማሳለፍ የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ ማድረግ አስፈላጊ በመሆኑ የአክሲዩኑ አባላት ሐምሌ 11/ 2013 ዓ.ም ፣እሑድ ልክ ከጧቱ 2፡30 ሰዓት በባሕር ዳር ከተማ፣ከቅዱስ ጊዩርጊስ ቤተክርስቲያን ወደ ፖሊ መስመር፣ ከአልማ ቢሮ ፊት ለፊት በሚገኘው በሰመር ላንድ ሆቴል አዳራሽ በሰዓቱ በግንባር/ በሕጋዊ ወኪል እንዲገኙልን በአክብሮት ጠርተነዎታል፡፡

አጀንዳዎች፡-

  1. የአክሲዮኑን የምስረታ ሂደት የሥራ ክንውን
  2. የአክሲዮኑን የመመስረቻና የመተዳደሪያ ደንብ ማፅደቅ/ የዳይሬክተሮች ቦርድና ሥራ አመራር መምረጥ
  3. የአክሲዮኑ ካፒታልና የእያንዳንዱ አባል የዕጣ መጠን
  4. በአክሲዩኑ በኩል የሚሸጥ ተጨማሪ ዕጣ ማፅደቅ
  5. ለ2014 ዓ.ም የበጀት ዓመት ሥራዎችንና በጀት ማፅደቅ
  6. የውጭ ኦዲተርን በተመለከተ

 

ማሳሰቢያ፡-

  • መታወቂያ ይያዙ
  • በሕጋዊ ወኪል የምትቀርቡ የውክልናውን ዋናና ኮፒ
  • ስብሰባው ለማካሄድ ምልአተ ጉባዔ ያስፈልገዋል